የጎደሬ ቡናና ቅመማ ቅመም እርሻ ልማታችን በሀገራችን የደቡብ ምዕራብ ክፍል በጋምቤላ ክልል በማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ አካባቢው ከባህር ጠለል በላይ ከ1,600 እስከ 2,100 ሜትር ከፍታ ባለው በትሮፒካል ሞቃታማ የአየር ንብረት የሚመደብ ሆኖ፣ የተፈጥሮ ደንና በርካታ ምንጮች እንዲሁም በዙሪያው በርካታ ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ካሉበት ውብ የተፈጥሮ መስህብ በተጎናፀፈ ስፍራ ላይ የሚገኝ የእርሻ ልማት ነው፡፡
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዳንጉር ወረዳ መተከል ዞን ኮታ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው ይህ የእርሻ ስፍራ በ3231 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ልማት ነው፡፡ ከባህር ጠለል በላይ 1000-1200 ሜትር ከፍታ፣ 1236-1928 ሚሜ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን፣ እንዲሁም ከ16-320C አማካይ የሙቀት መጠን አለው፡፡ ደረቅ ወይም ከፊል ደረቃማ አካባቢ በሚባለው የአየር ሁኔታ ውስጥ ይካተታል፡፡ ይህም የአየር ንብረቱ ዘመናዊ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም አኩሪ አተርና ሌሎች የእህል ሰብሎችን ለማልማት ምቹ እንዲሆን አድርጎታል።
አዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ይህ የቡና ማቀነባበሪያና ማከማቻ ማዕከላችን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ደረጃን ያሟላና በሰአት ከ5.78 ቶን በላይ የማዘጋጀት አቅም ያለው፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት ነው። በዋነኛነት ጎደሬ ከሚገኘው የኩባንያው የቡና እርሻ ልማት ጋር ትስስር እንዲፈጥር ሆኖ የተቋቋመው ይህ ማእከል በአሁኑ ሰዓት ከራሳችን የቡና እርሻ የሚመረተውን ቡና ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የውጭ ደንበኞችም ጭምር የማቀነባበር አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ተመራጭ ማዕከል ሆኗል፡፡
ቡና ወደ ውጭ መላክ ይህ ዘርፍ አንዱና ዋነኛው የንግድ ዘርፋችን ሲሆን ኢትዮጵያ የምትታወቅበትን ቡና ለአለም ገበያ በማቅረብ የቡና ኢንዱስትሪን በማጎልበት ረገድ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ በምናቀርበው ጥራት ያለው ቡና ኩራት ይሰማናል፣ ጥራት፣ ፍትሃዊ የንግድ አሰራርን በመከተላችን እና በዘላቂ አስተማማኝ አቅርቦት ምክንያት በአለም አቀፍ የቡና ገዢዎች ዘንድ መልካም ስምን አግኝተናል፡፡ በሁሉም የኤክስፖርት ሂደቶች ላይ ላይ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የኢትዮጵያ ቡና ከታወቀበት ልዩ ጣዕም ጋር እንዲደርስ በማድረግ ዘላቂ ለአገሪቱ የቡና ዘርፍ እድገት አስተዋፅዖ እናደርጋለን።
የጎደሬ ቡናና ቅመማ ቅመም እርሻ ልማታችን በሀገራችን የደቡብ ምዕራብ ክፍል በጋምቤላ ክልል በማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ አካባቢው ከባህር ጠለል በላይ ከ1,600 እስከ 2,100 ሜትር ከፍታ ባለው በትሮፒካል ሞቃታማ የአየር ንብረት የሚመደብ ሆኖ፣ የተፈጥሮ ደንና በርካታ ምንጮች እንዲሁም በዙሪያው በርካታ ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ካሉበት ውብ የተፈጥሮ መስህብ በተጎናፀፈ ስፍራ ላይ የሚገኝ የእርሻ ልማት ነው፡፡
የእርሻ ልማቱ የሚገኝበት ስነ-ምህዳር ከሁለት የደረቅ ወራት በስተቀር ዓመቱን በሙሉ በሚባል ደረጃ ዝናብ የሚያገኝ አካባቢ ሲሆን የእርሻ ልማታችን አጠቃላይ ይዞታ 2,976 ሄክታር መሬትን ይሸፍናል፡፡ ሙሉ ለሙሉ ለዘመናዊ ቡና እና የቅመማ ቅመም ልማት የተመቸ፣ በተፈጥሮ ሀብት በበለፀገ ቦታ ከፍተኛ ጥራት ላለው የቡና እና የቅመማ ቅመም ምርት ተስማሚ በሆነው ቦታ ላይ ድርጅታችን ደረጃውን የጠበቀ የማሳ እንክብካቤ፣ የሰብል አያያዝና አመራረት ሂደትን በመተግበርና በዘመናዊ የቡና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች በመጠቀም የቡና ልማት ስራውን ያከናውናል፡፡ ከፍተኛና ጥራት ያለው ምርት ለማግኘት ከሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች መካከል በሰዓት 12 ቶን መፈልፈል የሚችሉ የሁለት የእርጥብ ቡና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችና ዘመናዊ ሰው ሰራሽ የቡና ማድረቂያ ማሽንም ባለቤት ሲሆን በተጓዳኝም በሰዓት 6 ቶን የማበጠር አቅም ያለው የደረቅ ቡና ማቀነባበሪያም አለው፡፡ የእርሻው አመቺ የተፈጥሮ አቀማመጥ፣ ለም አፈር እና የአካባቢ ስነ ምህዳር ተስማሚነት ዘመናዊ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው ቡና እና ቅመማ ቅመም ለማምረት ጥሩ መሰረት ከመጣሉ ባሻገር ኩባንያው በቀጣይ ለሚሰራቸው ሌሎች መሰል ግብርና-ተኮር ፕሮጀክቶች አስተማማኝ ተሞክሮ ማበርከት ችሏል።