የጎደሬ ቡናና ቅመማ ቅመም እርሻ ልማታችን በሀገራችን የደቡብ ምዕራብ ክፍል በጋምቤላ ክልል በማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ አካባቢው ከባህር ጠለል በላይ ከ1,600 እስከ 2,100 ሜትር ከፍታ ባለው በትሮፒካል ሞቃታማ የአየር ንብረት የሚመደብ ሆኖ፣ የተፈጥሮ ደንና በርካታ ምንጮች እንዲሁም በዙሪያው በርካታ ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ካሉበት ውብ የተፈጥሮ መስህብ በተጎናፀፈ ስፍራ ላይ የሚገኝ የእርሻ ልማት ነው፡፡
በጣዕምና በምግብ ይዘቱ በታወቀቱ የዘይት ምርታችን ማዕድዎን ያጣፍጡ፡፡ ከምርጥ ንጥረ ነገሮች የተቀመመው እና በዘርፉ የካበተ ልምድና ክህሎት ባላቸው ባለሙያዎቻችን፣ በዘመናዊ ፋብሪካችን የተቀነባበረው የዘይት ምርታችን እጅግ ልዩ ጣዕም ብቻ ሳይሆን በምግብ ይዘቱም የበለፀገ ነው፡፡
ቤአኤካ የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚችል የተሽከርካሪ ጥገና ወርክሾፕ ያለው ሲሆን አሜሪካ፣ አውሮፓና ጃፓን ሰራሽ መኪኖችን ለመጠገን ሙሉ አቅም ያለው ግዙፍ ማዕከል ነው፡፡ በኢንሹራንስ ድርጅቶችና በሌሎች ተቋማት የሚመረጠው ጋራዣችን የመኪና ቀለም ቅብ፣ የተሽከርካሪ ኮምፒዩተር ሲስተም ጥገና፣ መካኒካልና ኤሌክትሪካል ስራዎችና ሌሎችንም በጥራትና በቅልጥፍና የሚሰራ ሲሆን በዘመናዊ የጥገና መሳሪያዎችና ግብአቶችም የተሟላ ነው፡፡
ፋብሪካው በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ የሚገኝ ሲሆን እያደገ ከመጣው የቀለም እና ቴራዞ ንጣፍ ፋብሪካ የጥሬ ዕቃ ፍላጎት ጋር ተያይዞ በቀን 120 ቶን የማምረት አቅም ያለውን የእብነበረድ እና ካልሲየም ካርቦኔት ቺፕስ መፍጫና ማሸጊያ ፋብሪካ አቋቁመናል። ፋብሪካችን ምርቶቹን ለፕላስቲክ (PVC) ፋብሪካዎች፣ ለሳሙና እና ዲተርጀንት ፋብሪካዎች፣ ለቀለም ፋብሪካዎች እና ለሌሎች ኢንዱስትሪዎች ግብአት እያቀረበ ይገኛል።