የጎደሬ ቡናና ቅመማ ቅመም እርሻ ልማታችን በሀገራችን የደቡብ ምዕራብ ክፍል በጋምቤላ ክልል በማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ አካባቢው ከባህር ጠለል በላይ ከ1,600 እስከ 2,100 ሜትር ከፍታ ባለው በትሮፒካል ሞቃታማ የአየር ንብረት የሚመደብ ሆኖ፣ የተፈጥሮ ደንና በርካታ ምንጮች እንዲሁም በዙሪያው በርካታ ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ካሉበት ውብ የተፈጥሮ መስህብ በተጎናፀፈ ስፍራ ላይ የሚገኝ የእርሻ ልማት ነው፡፡
ለደስታዎ ከፍተኛ ጥራት ያለው ባቄላ በጥንቃቄ የምናረጋግጥበት የኛን የባለሙያ ቡና ጽዳት እና ደረጃ አሰጣጥን ይለማመዱ። በትክክለኛ እና የላቀ ቴክኒኮች, ቆሻሻዎችን እናስወግዳለን እና ባቄላዎቹን በመጠን, በቀለም እና በመጠን እንከፋፍለን. ወደር የሌለው ጣዕም እና መዓዛ ያለው የላቀ የቡና ተሞክሮ እንድናቀርብ እመኑን።
ቡናን ለውጭ ገበያ የምናዘጋጅባቸው ማሽኖች በዋናነት አውሮፓ ሰራሽና ደረጃቸውን የጠበቁ ቴክኖሎጂዎች ሲሆኑ በተለይ ጀርመን ሰራት የሆኑት እነዚህ ማሽኖች በሰዓት 7.5 ቶን ቡና የማዘጋጀት አቅም ያላቸው ሲሆን በርካታ ቡና ላኪዎች እኛን በጽዳት፣ በፍጥነትና በምንጠቀመው ቴክኖሎጂ ዋናው ምርጫቸው እንድንሆን አድርጎናል፡፡ የማከማቻ ቦታችን አስተማማኝነት፣ ቅልጥፍናና ፍትሃዊ ዋጋ የተመራጭነታችን ሌሎች ምክንያቶች ናቸው፡፡
ይህ ተቋም በአዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን በተቀመጠው ደረጃ መሰረት በሰዓት ከ5.78 ቶን በላይ የማምረት አቅም ያለው እጅግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለትና ለውጭ ገበያ የሚውል የታጠበና የቅሽር ቡናዎችን በጥራት አዘጋጅቶ በማቅረብ ላይ ነው፡፡
ተቋሙ በዋነኛነት በጎደሬ ከሚገኘው የኩባንያው የቡና እርሻ ልማት ድርጅት ጋር ትስስር እንዲኖረው በኩባንያው ስር የተቋቋመ የአገልግሎት ዘርፍ ሲሆን አገልግሎቱን ከራሱ እርሻ ከሚመጣው የቡና ምርት ባሻገር ለእህት ኩባንያዎችና ለሌሎች የውጭ ደንበኞችም ጭምር በስፋትና በጥራት አገልግሎቱን እየሰጠ ይገኛል፡፡