የጎደሬ ቡናና ቅመማ ቅመም እርሻ ልማታችን በሀገራችን የደቡብ ምዕራብ ክፍል በጋምቤላ ክልል በማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ አካባቢው ከባህር ጠለል በላይ ከ1,600 እስከ 2,100 ሜትር ከፍታ ባለው በትሮፒካል ሞቃታማ የአየር ንብረት የሚመደብ ሆኖ፣ የተፈጥሮ ደንና በርካታ ምንጮች እንዲሁም በዙሪያው በርካታ ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ካሉበት ውብ የተፈጥሮ መስህብ በተጎናፀፈ ስፍራ ላይ የሚገኝ የእርሻ ልማት ነው፡፡
እርሻው በአማራ ክልል አዊ ዞን ጃዊ ወረዳ የሚገኝ ሲሆን እርሻው የዘይት ሰብሎችን፣የጥራጥሬና ጥራጥሬዎችን እንዲሁም ፍራፍሬ ለማምረት ያለመ ነው። በአሁኑ ጊዜ እርሻው ሙሉ በሙሉ አኩሪ አተር፣ ሩዝ፣ በቆሎ እና ማሽላ ለማምረት ያተኮረ ነው። ስለዚህ ስንዴ እና ሙግ ባቄላ በመስኖ የሚመረተው እንደ ተዘዋዋሪ ሰብሎች በበጋ ወቅት ነው።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዳንጉር ወረዳ መተከል ዞን ኮታ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው ይህ የእርሻ ስፍራ በ3231 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ልማት ነው፡፡ ከባህር ጠለል በላይ 1000-1200 ሜትር ከፍታ፣ 1236-1928 ሚሜ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን፣ እንዲሁም ከ16-320C አማካይ የሙቀት መጠን አለው፡፡ ደረቅ ወይም ከፊል ደረቃማ አካባቢ በሚባለው የአየር ሁኔታ ውስጥ ይካተታል፡፡ ይህም የአየር ንብረቱ ዘመናዊ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም አኩሪ አተርና ሌሎች የእህል ሰብሎችን ለማልማት ምቹ እንዲሆን አድርጎታል።
አዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ይህ የቡና ማቀነባበሪያና ማከማቻ ማዕከላችን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ደረጃን ያሟላና በሰአት ከ5.78 ቶን በላይ የማዘጋጀት አቅም ያለው፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት ነው። በዋነኛነት ጎደሬ ከሚገኘው የኩባንያው የቡና እርሻ ልማት ጋር ትስስር እንዲፈጥር ሆኖ የተቋቋመው ይህ ማእከል በአሁኑ ሰዓት ከራሳችን የቡና እርሻ የሚመረተውን ቡና ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የውጭ ደንበኞችም ጭምር የማቀነባበር አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ተመራጭ ማዕከል ሆኗል፡፡
በአማራ ክልል በአዊ ዞን በጃዊ ወረዳ 4ሺ ሄክታር መሬት የሚሸፍነው ይህ የተቀናጀ ሜካናይዝድ እርሻ ልማት የቅባት እህሎችን፣ ጥራጥሬዎችንና ሌሎች የብርዕና አገዳ ሰብሎችን እንዲሁም ፍራፍሬ ለማምረት ታስቦ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል። እርሻ ልማቱ ከአዲስ አበባ 595 ኪ/ሜ፣ ከባህርዳር ደግሞ 270 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ከባህር ጠለል በላይ 1100-1250 ሜ. በሆነ ከፍታ ላይ ይገኛል፡፡ የአካባቢው አማካይ የዝናብ መጠን 900-1100 ሚ.ሜ ፣ የሙቀት መጠኑ ደግሞ ከ17እስከ 32 ዲግሪ ሴልሽየስ ይሆናል፡፡ በአሁኑ ጊዜ እርሻው አኩሪ አተር፣ ሩዝ፣ በቆሎ እና ማሽላ ማምረት የሚችል ሲሆን በዓመት ሁለት ጊዜ ምርት መሰብሰብ ይቻል ዘንድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የመስኖ ዘዴ በመጠቀም ስንዴ እና ማሾ በደረቅ ወራትም በማፈራረቅ ዘዴ እንዲመረቱ እየተደረገ ይገኛል። በመሆኑም ከእርሻው የሚመረተው የቅባት እህል ከሌሎች ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በኮንትራት እርሻ ከሚመረተው ጋር በማዳበል ኩባንያው በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት፣ በሸገር ከተማ፣ በቡራዩ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የታጠቅ ኢንዱስትሪያል ዞን ውስጥ ለሚገኘው የኩባንያው የምግብ ዘይት ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ዘላቂ እና አስተማማኝ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ እንቅስቃሴ የሚያደርግ የእርሻ ልማት ተቋም ነው፡፡
የእርሻ ልማቱ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን፣ ዳንጉር ወረዳ ቆታ ቀበሌ ውስጥ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ በ3,231 ሄክታር መሬት ላይ የተጀመረ ነው፡፡ አካባቢው ከባህር ጠለል በላይ ከፍታው ከ1,000-1,200 ሜትር፣ አማካይ የዝናብ መጠኑ 1,236-1,928 ሚሜ፣ አማካይ የሙቀት መጠኑ ከ16-32 ዲግሪ ሴልሺየስ ሲሆን ደረቅ ወይም ከፊል በረሃማ አካባቢ በሚባለው ስነ ምህዳር ውስጥ ይካተታል፡፡ ይህም የአየር ንብረቱ ዘመናዊ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም አኩሪ አተርና ሌሎች የቅባት፣ የሰብልና የጥራጥሬ ሰብሎችን ለማልማት ምቹ መሆኑን ያሳያል።